‎በምስራቅ ጉራጌ ዞን "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ቃል ለዞን ማዕከል የብልፅግና ፓርቲ አባላት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ።

‎#ቡታጅራ| ታህሳስ 09/2018 ዓ.ም

‎በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን "በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እምርታ" በሚል መሪ ቃል ለዞን ማዕከል የብልፅግና ፓርቲ አባላት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።

‎አባላቱ በስልጠናው ማጠቃለያ በሰጡት አስተያየት እንደገለጹት የተሰጠው ስልጠና የአባሉን አቅም የገነባናየአባሉን ተነሳሽነትና ቁርጠኝነትን ያሳደገ የብልፅግና ፓርቲ እሳቤን ወደ ታለመለት ግብ ለማድረስ  ከፍተኛ ድርሻ የሚኖረው መሆኑን ገልፀዋል። 

‎ምስራቅ ጉራጌ ዞን ከተመሰረተ ሁለት ዓመቱ ብቻ ቢሆንም በወሳኝ የልማት ዘርፎች ውጤታማ መሆኑን ጠቅሰው ከዚህ በላቀ ሁኔታ ዞኑን እና የዞኑ ተቋማትን የብልፅግና ተሞክሮ ማዕከል ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት አስተያየት ሰጭዎቹ በተለያዩ የልማት መስኮች የመፈፀም አቅምና የስራ ባህል ለውጥ የመጣበት መሆኑን ተናግረዋል። 

‎በየደረጃው ያለው ፈፃሚ  በችግር ያለመታሰር በሀገራዊ ህልሞች ላይ ትኩረት በማድረግ ተሞክሮዎችን በመቀመር ማስፋት ከአባላት ይጠበቅብናል ብለዋል። 

‎ባለሙያዎች በሁሉም ዘርፍ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የስራ አካባቢንና ስራን እንዲሁም እራስን በኃላፊነትና በተጠያቂነት  መምራት፤ በሁሉም መስክ የሚታይ የስራ ባህል ለውጥ ማምጣት ላይ ትኩረት ማድረግ ተገቢ ስለመሆኑ ሰልጣኞቹ ተናግሯል።

‎"በመደመር መንግስት  ዕይታ ፤ የዘርፎች እመርታ" ሥልጠና ማጠቃለያ የፓርቲያችን ፕረዚዳንት  ዶ/ር ዐብይ አህመድ  ያስቀመጡትን አቅጣጫ መነሻ ያደረገ ዋና ዋና ግቦችን የያዘ ዕቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

 

22ኛው ዓለም አቀፍ የጸረ-ሙስና ቀን በወራቤ ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው

ታህሳስ 9/2018 ዓ.ም

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል"ትውልድን በስነ ምግባር ተቋምን በአሰራር " በሚል መሪ ሀሳብ 22ኛው ዓለም አቀፍ የጸረ-ሙስና ቀን በወራቤ ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው

በመርሐ ግብሩ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፋጤ ስርሞሎ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አቡቶ አኒቶ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክላስተር አስተባባሪዎች፣የክልሉ የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ማሞ ቴጋ፣ከክልል፣ከዞኖች እና ከልዩ ወረዳዎች የተውጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

 

   በምስራቅ ጉራጌ ዞን  "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል ርዕስ ለዞን ማዕከል የብልፅግና ፓርቲ የአባላት ስልጠና መካሄድ  ጀምሯል።

#ቡታጅራ| ታህሳስ 08/2018 ዓ.ም

በብልፅግና ፓርቲ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የምስራቅ ጉራጌ ዞን የብልፅግና ፓርቲ  አባላት "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል ርዕስ ለዞን ማዕከል የብልፅግና ፓርቲ አባላት ስልጠና መሰጠት  ተጀምሯል።

ስልጠናው "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።

ስልጠናው የአባሉን እውቀት፣ ክህሎትና አቅም የሚገነቡ ልዩ ልዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚዳሰሱበት መሆኑ ተገልጿል።

 

 

 "ትውልድ በስነ-ምግባር ተቋም በአሰራር" በሚል መሪ ቃል የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር የዓለም የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና  ቀን እያከበረ  ይገኛል።

ታህሳስ 07/2018 ዓ.ም(ቡታጅራ)

የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር በአለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በሀገራችን ለ21ኛ በክልላችን ለ3ኛ ጊዜ የሚከበረው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቀን "ትውልድን በስነ-ምግባር ተቋም በአሰራር" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች እያከበረ ነው።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት እንዳሉት ቀኑን በየዓመቱ ስናከብር  አስተውለን ቃላችንን አድሰን ተቋም በስነ ምግባር መምራት እንድንችል ነው ብለዋል።

መልካም የሆኑ ባህሎችን ማጉላት ያስፈልጋል ያለት አስተዳዳሪው ሙስናን ታግለን ሀገርን መገንባት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

ሙስናን መታገል የእለት ተእለት ተግባራችን በማድረግ ሙስና ላይ የተሳተፉ አካላትን ማስተማር፤ ማረምና ማጋለጥ እንደሚገባ   አስረድተዋል።

ትግሉን በማቀጣጠል ዞኑን ከሙስና ነፃ ማድረግ አለብን ያሉት አስተዳዳሪው ትውልድ ልማትን በማያደናቅፍ መልኩ በመቅረፅ የተሻለ ኢትዮጵያ መፍጠር ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ እንዳልካቸው ጌታቸው፤ የዞኑ ም/አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሱ አበጋዝ፤ የዞኑ አጠቃላይ  አመራሮች እና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

ዘገባው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ነው።

 

 

"ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ የተከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን  ውጣታማ በሆነ መልኩ  መከበሩ ተገለፀ።

#ቡታጅራ| ታህሳስ 06/2018 ዓ.ም

የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር የ20ኛውን የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አፈጻጸም ግምገማ አካሄዷል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን  "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ሀሳብ የተከበረው 20ኛው የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ቅንጅትና መናበብ ተሞክሮ መሆን የሚችል በዓል መከበሩ ገልፀዋል።

ከቅድመ ዝግጅት ስራዎች ጀምሮ  የማህበረሰባችን እንግዳ ተቀባይነት በሚመጥን መልኩ ለማክበርና እንግዶችን ለመቀበል በትኩረት በተሰሩ ስራዎች ውጤታማ በዓል በማድረግ ማለፉን አንስተዋል።

እንደ ሀገር ስኬታማ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በማክበር ክልሉ አድናቆትን የተቸረውና ለሌሎችም ልምድና ተሞክሮ መሆን እንደቻለ አመላክተዋል።

ህዝብና  አመራር በቅንጅት በመስራቱ በአሉ  ስኬታማ እንደነበር ጠቅሰው በየደረጃው ድርሻቸው ለተወጡ ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ እንዳልካቸው ጌታቸው በበኩላቸው 20ኛ  የኢትዮጵያ የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ደማቅና ስኬታማ በዓል ተከብሯል ብለዋል።

ዋና አፈ ጉባኤው የዞናል በዓል አከባበርና የእግዳ አቀባበል ሂደት  አስመልክቶ የተፈፀሙ ዝርዝር ተግባራት ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት  ዞኑ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መግቢያ በመሆኑ ዞኑን አቋርጠው ወደ ሆሳዕና ለሚያልፋ የ8 ክልል ልዑካን ቡድን በቡታጅራ ከተማ  የዞኑ ማህበረሰብ በሚመጥን መልኩ እንግዶችን ተቀብለን መሸኘት ችለናል ብለዋል። ለዚህም አጠቃላይ የዞኑ ህዝብ፣ አመራሮች ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ፣ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የፀጥታ አካላትና  የዞኑ የባህል ቡድን ላደረጉት አስተዋፆ ምስጋና አቅርበዋል።

የምስራቅ ጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ  አቶ መሰለ ጫካ በዓሉ ህዝብና አመራር ከተቀናጀ ሁሉም ነገር ማሳካት እንደሚቻል ያሳየና ስኬታማ እንደነበር ገልፀዋል።

በዓሉ የማህበረሰብ አንድነትና አብሮነት እንዲሁም እንግዳ ተቀባይነት ማሳየት ያስቻለ ሁነት በማከናወን ውጤት የተገኘበት እንደነበረም አንስተዋል።

በቀጣይ በሁሉም መድረኮች አመራሩ በመናበብ መሰል መድረኮች ለማሳካት የነበሩ ጉድለቶችን በማረም መልካም ልምዶችን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።

በመድረኩም የዞኑ አስተባባሪዎች፣ የዞኑ ጠቅላላ አመራር፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አስተባባሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በአጠቃላይ የበአል አከባበሩ ውጤታማ እንዲሆን ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ አስከ ፍፃሜው በቅንጅት የተሰራው ስራ ውጤታማ እንደነበረና  ለቀጣይም ትምህርት የሚወሰድበት መሆኑን  በመድረኩ አስተያየት የሰጡ ተሳታፊዎች ገልፀዋል ።            

             

           

  መግለጫ 

 

‌‎በቡታጅራ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን ገፅታ የቀየረ፣ ለነዋሪዎችና ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን የፈጠረ እና ፕሮጀክት ጀምሮ የመጨረስ ብቃት የታየበት መሆኑን ሰልጣኞች ገለፁ
‎ህዳር 16/2018ዓ.ም 

‎የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛና መካከለኛ ሰልጣኝ አመራሮች በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ስራ በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

‎በጉብኝቱ ተገኝተው አስተያየታቸውን የሰጡን ሰልጣኞች እንደገለፁት የቡታጅራ ከተማ የኮሪደር ልማት የአመራርና የህዝቡ ቅንጅታዊ ስራ የታየበት እጅግ ውብና ማራኪ እንዲሁም ፕሮጀክት ጀምሮ የመጨረስ ብቃት የታየበት መሆኑን ገለፀዋል።

‎ስልጠናውና ጉብኝቱ ዕውቀትና ልምድ የተገኘበት ሁሉም በተሰማራበት መስክ በቁጭት ተነሳስቶ በላቀ ደረጃ በአካባቢው በመትጋት የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ እንዲቻል ከፍተኛ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው መረዳት ተችሏል።

መረጃው የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ሚዲያ ዘርፍ ነው

 

 

 

 

የም/ጉራጌ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ የአቶ መሰለ ጫካ መልዕክት


ፓርቲያችን ብልጽግና በኢህአዴግ ዘመን የነበሩ የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶችን እና አጋር በሚል ሲጠሩ የነበሩ የፖለቲካ ድርጅቶችን በማካተት አቃፊ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሥርዓት የሚገነባ ‹‹ የብልጽግና ፓርቲ›› የሚሰኝ ኅብረ ሀገራዊ ፓርቲ ሆኖ የተቋቋመ ፓርቲ ነው፡፡ የፓርቲያችን ጥቅል ዓላማ የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው፡፡ ብልጽግና ስንል ፈርጀ ብዙ ትርጓሜን አዝሎ የኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ እና ማኅበራዊ ገጽታ ያለው ነው፡፡

ኢኮኖሚ ብልጽግና ፣ የሕዝቦች መሠረታዊ ፍላጎቶች በተገቢና በዘላቂነት ለማሟላት የሚያስችል ፈጣን እና ሁለንተናዊ ዕድገትን በማስመዝገብ፣ ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነትን ያለው ኢኮኖሚ በመገንባት ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥና የህዝቦችን ድህነትና ኋላ ቀርነትን ለመቅረፍ መቻልን ያካተተ ነው፡፡

የፖለቲካ ብልጽግና ስንል ለዴሞክራሲ ባህል ማበብ አስፈላጊ የሆኑ ተቋማትን በመገንባት፣ የሕዝቦች ነጻነትና እኩልነት ተረጋግጦ ሁሉም ኢትዮጵውያን ሰብአዊና ዴሞክሲያዊ መብቶቻቸው ተከብረውላቸው የሚኖሩባትን፣ ኅብረ ሀገራዊ አንድነቷ የተረጋገጠ፣ ፌደራላዊት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ጽኑ መሠረት ላይ ማቆም ነው፡፡

ማኅበራዊ ብልጽግና፤ መልካም ሀገራዊ ወጎችን፣ ዕሴቶችን እና ባህሎችን በማዳበር በሥነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ማፍራት፣ በአካልና በአዕምሮ የዳበረ ጤናማ ዜጋ መፍጠር፣ ከአስከፊ ማኅበራዊ ችግር የተጠበቀ ኅብረተሰብ መገንባት እና በሕዝቦች መካከል አዎንታዊ ሰላም በመፍጠር ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ ማለት ነው፡፡

ክልላችን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና ዞናችን ምስራቅ ጉራጌ ዞን በ2015 ዓ/ም በመጨረሻው ነሐሴ ወር ላይ ተደራጅው ስራ የጀመሩ ቢሆንም ከተደራጁ ሁለት ዓመት እንኳን ሳይሞላ የክልሉን ብሎም የዞናችንን ህዝብ ተጠቃሚ ማድግ ያስቻሉ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን ማከናወን የተቻለበት እንዲሁም በቀጣይም በአጭር እና በረጅም ግዜ የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የሀገራችን ኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ዕውን ለማድረግ እተጋን እንገኛለን፡፡

ስለሆነም በዞናችን የምትገኙ የፓርቲያችን አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም መላው የዞናችን ህዝቦች የፓርቲያችን የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ዕውን የማድረግ ራዕይ እንዲሳካ ለማስቻል የተመዘገቡ መልካም የልማት ውጤቶች በላቀ ደረጃ ቀጣይነታቸው እንዲረጋገጥና በትጋታችን የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ዕውን ለማድረግ ሁሉም በየተሰማራበት መስክ እንዲተጋና ለውጤት እንዲሰራ አደራ በማለት መልዕክቴን ለማስተላለፍ እወዳለሁ፡፡